Federal Judicial Administration Council Secretariat

የፌደራል ዳኞች ጥቅማጥቅም ስልጠናና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ዳይሬክተር

  • የዳይሬክቶሬቱን ተግባራት ያቅዳል፣ ያደረጃል፣ ይመራል፣ ይከታተላል፣ ይደግፋል፣ ይወስናል ይቆጣጠራል፣
  • ከጽ/ቤቱ ስትራቴጂክዊ ዕቅድ የተመነዘረ ዓመታዊ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ አፈጻጸሙን ይከታተላል፣ ይገመግማል፣
  • ዳኞች የሚገባቸውን ጥቅማጥቅም እንዲያገኙ ጥናትናምርምሮችንያካሄዳል፣በጥናት የተደገፈ የውሳኔ ሐሳብ ለጉባኤው ጽ/ቤት ያቀርባል፣
  • የዳኞችጥቅማጥቅም፤ሌሎች የአስተዳደር ጉዳዮች የተሟላ የህግ ማዕቀፍ እንዲዘጋጅላቸው ያደርጋል፣አስተዳደራዊ ስራዎች በአግባቡ መፈጸማቸውን ይከታተላል፡፡
  • የዳኞች ምልመላ በተመለከተ መመሪያዎችንና ማንዋሎችን አዘጋጅቶ እንዲጸደቅ ያደርጋል፣ አፈፃፀሙን ይከታተላል፣
  • የእጩ ዳኞች ምልመላ ከምዝገባ እስከ ሹመት ድረስ ያለውን ሂደት ይካታተላል
  • የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ተሞክሮችን ይዳስሳል፤ጠቃሚ የሆኑትን በስራ ላይ እንዲውሉ ይደርጋል
  • በተቋም ሜሪቲን የተከተለ የሰው ሀብት ምልመላና መረጣ እንዲከናወን ያደርጋል፣ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅሞችና አገልግሎቶች ሳይዛቡ ሥራ ላይ እንዲውሉ እንዲሁም ምቹ የሥራ አካባቢ እንዲኖር ያደርጋል፣
  • አዲስ ለሚቀጠሩ ሠራተኞች ስለ መንግሥት መመሪያዎችና ደንቦች እንዲሁም ተቋሙ ስለተቋቋመበትና ስለሚጠበቅበት ውጤት እንዲሁም ስለ መሥሪያ ቤቱ ልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች ኃላፊነት የማስተዋወቂያ ስልጠና (`Inducation) እንዲሰጥ በማድረግ ወደ ሥራ እንዲሰማሩ ያደርጋል፣
  • የተቋም ሠራተኞች መንግሥት በወጣው የምዘና ስርዓት መሠረት በየወቅቱ እንዲመዘኑ ያደርጋል፣ በምዘናው ውጤት መሠረትም ቀጣይ ተግባራትን ያከናውናል፣
  • በመንግሥት ሠራተኞች መመሪያዎችና ደንቦች መሠረት በተቋሙ  ልዩ ልዩ የቅጥር፣ የደረጃ ዕድገት፣ ዝውውር፣ የዲስፕሊን፣ የቅሬታ ማስተናገጃና እንዲሁም ሌሎች አግባብነት ያላቸው  ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙና ተግባራዊ እንዲሆኑ ይከታተላል፡፡
  • በተቋሙ የበላይ ኃላፊዎች በሚሰጠው የሥልጣን ውክልና መሠረት በሰው ሃብት ሥራ አመራርና አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ይሰጣል፣ ወይም የሚሰጡ ውሳኔዎችን ተግባራዊነት ይከታተላል፣
  • የዳኞች እና የሠራተኞች የግል ማህደሮች ተሟልተውና ዘመናዊ ሆነው እንዲያዙ ክትትል ያደርጋል፣
  • የመረጃ አያያዝ ሥርዓቱን በቴክኖሎጂ እንዲደገፍ የሚያደርግ ስርዓት ይዘረጋል፣በአግባቡ አገልግሎት እየሠጠ መሆኑን ያረጋግጣል፣
  • የሠራተኞችን እና የዳኞች አጠቃላይ እስታስቲካዊ መረጃዎች መያዙን ይከታተላል
  • ወቅታዊ የስራ አፈጻጻም ሪፖርት ለሚመለከተው አካል ያቀርባል፡፡
  • ከሌሎች የጽ/ቤቱ የስራ ክፍሎች ጋር በመተባበር ይሠራል፣