Federal Judicial Administration Council Secretariat

የፍርድ ሥራ ምርመራ እና የዳኞች ዲሲፕሊን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ተግባራት

 በዳኞች ላይ የቀረቡ የዲሲፕሊን አቤቱታዎችን ይቀበላል፤
 የቀረቡትን የዲሲፕሊን አቤቱታዎች መሠረት በማድረግ ቅሬታ የቀረበባቸውን መዛግብት ከየ ፍርድ ቤቶች መዝገብ እንዲመጣ ያደርጋል፤
 መዝገቦች በጥንቃቄ መያዛቸውንና መመለሳቸውን ይከታተላል፤ይቆጣጠራል፤
 የዳኞችና የጉባኤ ተሿሚዎች የስነ ምግባር መረጃ ይይዛል፤በሚመለከተው አካል ሲጠየቅ ይሰጣል፡፡
የፌደራል ዳኞች የስነምግባርና ዲሲፕሊን ጉዳዮች ኮሚቴ ተግባር

በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ጽ/ቤት አማካኝነት የሚቀርቡለትን የዲሲፕሊን መዛግብት ቅሬታውንና ቅሬታ ከቀረበበት የፍርድ ቤት መዝገብ ጋር ምርመራ በማድረግ በፌደራል ዳኞች የሥነ-ምግባርና የዲሲፕሊን ክስ ሥነ-ሥርዓት ደንብ ቁጥር 3/2014 አንቀጽ 25 (3) (ሀ) መሠረት የምርመራ ሪፖርት /የውሳኔ ሃሳብ ለፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ያቀርባል::